የሥላሴ አጠያያቂ ምስጢር

ጸሃፊ፡-                           ፓስተር ኤልያስ ሽባባው (seeliyahu@gmail.com) 

የታተመበት ቦታና ዓ.ም.፡-        2008 ዓ.ም.፣ አዲስ አበባ 

አሳታሚ፡-                        የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንፖ.ሳ.ቁ. 4442፣ ስልክ 251-114-660086 

አታሚ፡-                          ሪላ አታሚዎች                   የገጽ ብዛት፡-        347

መጽሐፉ አስራ አምስት ክፍሎች ተከፋፍሎ የቀረበ ነው፡፡ መጽሐፉ የጥናታዊ ጽሁፎች መድብል አይነት ሲሆን በርካታ ቁምነገሮችን ያዘለ ነው፡፡ በምዕራፍ ሁለት ላይ የሥላሴን ትምህርት ብዥታዎች ነቅሶ ያወጣና በምዕራፍ ሦስት ላይ የሥላሴ አማንያን ‹‹ሥላሴ›› ምንም እንኳ ሦስትነትን ቢገልጽም አንድ አምላክ እንጂ ሦስት አማልክት አናመልክም ቢሉም የተለያዩ የእምነቱ አስተማሪዎች የጻፏቸውን መጻሕፍት በማጣቀስ እምነቱ በሦስት አማልክት ወደማምለክ እንደሚስባቸው በዝርዝር ያቀርባል፡፡ 

ምዕራፍ አራት እና ምዕራፍ አምስት በአረማውያን አስተምህሮ ውስጥ ያሉትን የትምህርተ ስሉስ አይነቶችን ይዘረዝራሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል የባቢሎናውያን ሥሉስየአሶራውያን ስሉስየግብጻውያን ሥሉስየግሪኮች ሥሉስየሮማውያንየሂንዱየቡድሂዝምየስዊድንየቻይናየፋርስየጃፓንየሽንቶየሜክሲካውያንየአይሪሽየብሪታንያየዓረብ ሴት እና ሌሎች የአረማውያን የሥሉስ አምልኮ አይነቶች ይገኙበታል፡፡ ታዋቂው የግሪክ ፈላስፋ ፕሌቶም የአረማውያን ሥላሴ ትምህርት አባት እንደሆነ በማስረጃ ተደግፎ ቀርቦአል፡፡  

የመጽሐፉ ዋና ርዕሰ-ጉዳይ በክርስትናው ዓለም ያለው የትምህርተ ሥሉስ አስተምህሮ ከእንደነዚህ አይነት የአረማውያን አስተምህሮዎች ሾልኮ የገባ እንጂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መነሻ ያለው አለመሆኑን በማሳየት ሰዎች ነፍሳቸውን እንዲያድኑ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረው አንድ ብቸኛ አምላክ ብቻ እንዳለ እንዲረዱና እንዲያምኑ ለመርዳት ነው፡፡ ስለሆነም የአረማውያን አስተምህሮ በክርስትና ላይ ያሳደራቸውን ተጽዕኖዎችሥላሴ በክርስትናው ዓለም እንዴት እንደተከሰተመጽሐፍ ቅዱስ ግን ስለ አንድ ብቸኛ አምላክ ብቻ በግልጽ እንደሚያስተምርበምድር ላይ ሥላሴ የማይታመንበት ጊዜ እንደሚመጣየመጽሐፉ ጸሃፊ ደግሞ ለምን በሥላሴ እንደማያምኑ ያስቀመጧቸው 101 ምክንያቶች እና ሌሎችም ከርዕሱ ጋር የተያያዙ በርካታ አስተማሪ ቁም ነገሮች ተካትተዋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ ቢሾፕ ደጉ ከበደ በመቅድሙ ላይ ‹‹መጽሐፉ በሽፍንፍን የሰውን አዕምሮ አስረው የያዙ መልስ አይገኝላቸውም የተባለላቸውን ጥያቄዎች መልስ በመስጠት ሰው ማየት ያለበትን እንዲያይ ያስችላል የሚል ብርቱ እምነት አለኝ›› በማለት ጽፈዋል፡፡

Scroll to Top