በስልጠናው ላይ ከተሳተፉት አገልጋዮች እንደተሰማው ጌታ ኢየሱስ ልባቸውን በቃሉ ነክቶ ከአሁን በኋላ የወንጌል አገልግሎትን እንደ አዲስ እንደሚጀምሩ እስኪሰማቸው ድረስ ታላቅ የእግዚአብሔር ጉብኝት የፈሰሰበት ፕሮግራም ነበር፡፡ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተካሄደው ብዙ ምዕመናን የተሳተፉበት ኮንፍረንስ ከሐምሌ 23-25/2013 ዓ.ም የተደረገ ሲሆን ሐዋርያት የሰበኩት ወንጌል በታላቅ ኃይል ተሰብኮ ልባቸው የተነካ 117 አዳዲስ ነፍሳት ለኃጢአታቸው ስርየት በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠምቀዋል፡፡ በጉባኤው ላይ ከፍተኛ የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴ የነበረ ሲሆን ከ200 በላይ በሚሆኑ ሰዎች ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ወርዶ፣ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው በልሳን ተናግረዋል፡፡